አዲስ ዘመን ቅዳሜ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም
ግልጽ የጨረታ ማሰታወቂያ ቁጥር 04/2018
በአብክመ በምሥራቅ
ጎጃም ዞን የእኔዴድ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለወረዳ ባለበጀት መ/ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት የተለያዩ
የመኪና ዕቃዎች ግዥ፤ ሎት 2 የተለያዩ የእንስሳት መድኃኒትግብዓት ግዥ ሎት 3 የመኪና ጎማ ግዥ ሎት 04 የቤት ክዳን ቆርቆሮ
ግዥ ከSL-KFW በተገኘ የገንዘብ ድፍ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። እንዲሁም የተለያዩ ብረታ ብረቶችንና ያገለገ
·የመኪና ባትሪዎችን ደግሞ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር
የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- የተለያዩ
ብርታ ብረቶችን ለመግዛት ፍላጎት ያለው ማንኛውም ግልሰብም ሆነ ድርጅት ጋዜጣው በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር ለ15
ተከታታይ ቀንና እስከ 16ኛው ቀን 3፡30 ድረስ ብረታ ብረቶችን የሚገዙበትን ዋጋ በበሙላት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት
አለበት፡፡
- የጨረታ
ሰነዱን የማይመለስ 100.00/አንድ መቶ ብር/ በጥሬ ገንዘብ ወይም በመ/ቤታችን የገቢ ደረሰኝ በመሂነ ገቢ በማድረግ ሰነዱን መግዛት
የሚችሉ ሲሆን የሚሸጡ ብረታ ብረቶችን ዝርዝር መገለጫ ከመጫረቻ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ብረታ ብረቶችን
ለመግዛት የሚወዳደሩ ተወዳዳሪዎች ለሚወዳደሩበት ጥቅል ዋጋ ብር 3000.00/ ሶስት ሽህ ብር/የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ
በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና አለያም በመ/ቤታችን የገቢ ደረሰኝ በመሂ 1 ገቢ አድርጎ
ወይም በአነደድ ወረዳ የወረዳ በጀት ማስፈጸሚያ አካውንት ቁጥር 1000091375048 በማስገባት ሰነዱን አያይዞ ማቅረብ አለበት፡፡
- ብረታ ብረቶችን
ተወዳድሮ ያሸነፈው ግለሰብ ወይም ድርጅት ያሸነፈባቸውን ብረታ ብረቶች አሸናፊ መሆኑ በታወቀበት ቀን ካሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ 25% ክፍያውን ከፍሎ ቀሪውን
ገንዘብ ደግሞ በ3 ቀን ውስጥ ክፍያ አጠናቆ ብረታ ብረቶችን ጨርሶ ማንሳት ያለበት ሲሆን ከ3 ቀናት በኋላ ብረታ ብረቶችን ባለማንሳቱ
ምክንያት ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር መ/ቤታችን ተጠያቂ አይሆንም፡፡
- የሚሸጡ
ብረታ ብረቶችን ብዛት በኪግራም ከመጫረቻ ሰነዱ ማግኘት የሚቻል ሲሆን የኪ/ግራሙ መጠን በሽያጭ ወቅት ሲመዘን በጨረታ ሰነዱ ከተቀመጠው
በላይ ቢሆን ለአሸናፊው አካል ተደምሮ የሚሸጥ ይሆናል፡፡
በሎት ዐ1፤
በሎት ዐ2፤ በሎት ዐ3 እና በሎት 4 ዕቃዎች ደግሞ
1 በዘመኑ
የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ወረቀት ማቅረብ የሚችል
2. ከሎት
o2 ውጭ ያሉት ሎቶች የግዥ መጠኑ ከብር 200000.00/ሁለት መቶ ሽህ ብር /በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /የቫት ከፋይነት
የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው
3. ተጫራቾች
በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትንና ሌሎች ማስረጃዎች ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው።
4 የሚገዛውን
ዕቃ ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከመጫረቻ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
5. ተጫራቾች
የጨረታ ሰነዱን ለእያንዳንዱ ሎት ብር 100.00/አንድ መቶ ብር/በጥሬ ገንዘብ ወይም በመ/ቤታችን የገቢ ደረሰኝ በመሂ 1 ገቢ
በማድረግ ወይም በአነደድ ወረዳ የወረዳ በጀት ማስፈጸሚያ አካውንት ቁጥር 1000091375048 ላይ ገቢ በማድረግ ሰነዱን መግዛት
ይችላል።
6.ተጫራቾች
የጨረታ ማሰከበሪያ ዋስትና ቢድ ቦንድ ለሚወዳደሩበት ጥቅል ዋጋ ለሎት1. 10000.00/ አስር ሽህ ብር/፤ ለሎት 2.
5000.00/አምስት ሽህ ብር፤ ለሎት 3 3000.00/ ሶስት ሽህ ብር/ ለሎት 4 ብር 1000.00/ አንድ ሽህ ብር/በባንክ በተረጋገጠ
የክፍያ ትእዛዝ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና አለያም በመ/ቤታችን የገቢ ደረሰኝ በመሂ ı ወይም በአነደድ
ወረዳ የወረዳ በጀት ማስፈጸሚያ አካውንት ቁጥር 1000091375048 ላይ ገቢ በማድረግ ሰነዱን አያይዞ ማቅረብ አለበት፡፡
7 ማንኛውም
ተጫራች ሃሳቡን ዋናና ቅጅ በማለት ኦርጅናሉን ለብቻ ኮፒውን ለብቻ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማድረግ ስሙን፤ፊርማውንና ማህተሙን
በማሳረፍ አነደድ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ግቢ በሚገኘው ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 03 በተዘጋጀው
ጨረታ ሳጥን ዘውትር በስራ ሰዓት ጨረታው በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀንና እስከ 16ኛው ቀን 3፡30 ድረስ
ማስገባት አለበት።ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ16ኛው ቀን 3፡30 ታሽጎ 4፡30 ላይ ይከፈታል። የሥራ
ቀን ካልሆነም በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በጨረታ መክፈቻ ሰዓቱ ባይገኙም
መ/ቤቱ ጨረታውን የመክፈት መብት ያለው ሲሆን በጨረታ መክፈቻ ቀንና ሰዓት ያልተገኙ ተወዳዳሪዎች በተላላፈው ውሳኔ ተገዥ ይሆናሉ፡፡
8 በጨረታ
ሰነዱ ላይ የማብራሪያ የማሻሻያ ጥያቄን በተመለከተ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን ድረስ ማቅረብ ይቻላል፡፡
9 አሸናፊው
አካል ያሸነፈባቸውን ዕቃዎች ጠቅላላ ወጭውን በመሸፍን አነደድ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ድረስ የማቅርብ ግዴታ አለበት። ለሁሉም ሎቶች
ለውል መያዣ የሚፈለጉ ወጭዎችን አሸናፊው አካል የሚሸፍን ይሆናል።
10 ግዥ ፈጻሚው
አካል ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን በጨረታው መሰረዝ ምክንያት ለወጣው ወጭ ግዥ ፈጻሚው አካል
ተጠያቂ አይሆንም። ግዥ ፈጻሚው አካል ግዥውን 20% መቀነስም ሆነ መጨመር ይችላል።
11 ውድደሩ
የሁሉም ሎቶች በጥቅል ዋጋ ስለሚታይ ተጫራቾች በአንድ ሎት ያሉትን ዝርዝር ዕቃዎች ሁሉንም ዋጋ መሙላት ያለባቸው ሲሆን ግዥ ፈጻሚው
አካል ካወጣው ስፔስፊኬሽን ውጭ በራሱ ስፔስፊኬሽን የሞላ ተወዳዳሪ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
12. በውድድሩ
አሸናፊ የሆኑ ተወዳደሪዎች ዕቃውን ማቅረብ ያለባቸው ውል ከያዙበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር በ5 ቀን ውስጥ ማቅረብ አለባቸው። በማንኛውም
ግዥ ለእቃዎች ከብር 20000.00/ ሃያ ሽህ በላይ ለአገልግሎት ግዥ ደግሞ 10000.00/አስር ሽህ /በላይ ለሚሆኑ ግዥዎች አቅራቢው
ከሚፈጸምለት ክፍያ ላይ 3% ቅድመ ግብር/ዊዝ ሆልድ ተቀንሶ የሚቀር ሲሆን በውል አፈጻጸም ወቅት የዋጋ ማስተካከያ ማድረግ አይፈቀድም
።
13 ግዥ ፈጻሚው
መ/ቤት በወጡት በሁሉም ሎቶች የቅድሚያ ክፍያ የማይሰጥ ሲሆን ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለገ አነ/ወ/ ሲ/ሰ/ጽ/ቤት ውስጥ በሚገኘው
ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በአካል ወይም በስልክ ቁጥራችን 0913271823
/0946088403 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
በአብክመ ምሥራቅ ጎጃም ዞን የአነደድ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት